1 ቁጥር - ታኅሣስ ፪ሺህ ፭ ዓመተ ምሕረት DECEMBER 2012 ezralit@gmail.com ጤና ይስጥልኝ፤ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን። በዚህ የ2012 የመጨረሻ ስርጭት አንድ መጣጥፍ ብቻ አቅርቤአለሁ። እግዚአብሔር ዝም የሚልባቸው ጊዜያት አሉ። ለምክንያትና ለሥራው፥ ለምክሩና ለክብሩ ሲል ዝም ይላል። እግዚአብሔር ሲናገር በተናገረው እንደሚከበር ዝምታውም የተከበረ ነው። በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ...
More
1 ቁጥር - ታኅሣስ ፪ሺህ ፭ ዓመተ ምሕረት DECEMBER 2012 ezralit@gmail.com ጤና ይስጥልኝ፤ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን። በዚህ የ2012 የመጨረሻ ስርጭት አንድ መጣጥፍ ብቻ አቅርቤአለሁ። እግዚአብሔር ዝም የሚልባቸው ጊዜያት አሉ። ለምክንያትና ለሥራው፥ ለምክሩና ለክብሩ ሲል ዝም ይላል። እግዚአብሔር ሲናገር በተናገረው እንደሚከበር ዝምታውም የተከበረ ነው። በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ በትንቢተ ሚልክያስ እና በማቴዎስ ወንጌል መካከል ባዶ ገጾች የሉም። ነገር ግን በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ ውስጥ በነዚህ ሁለት መጽሐፎች መካከል ‘የዝምታ ዘመናት’ ተብሎ የሚታወቅ የ400 ዓመታት ክፍተት ይገኛል። በሚልክያስ ከተናገረ በኋላ “በመጀመሪያ ቃል ነበረ” የተባለው ቃል ራሱ ሥጋ ለብሶ እስከመጣበት ዘመን ድረስ ከእግዚአብሔር የተላለፈ የተጻፈ ቃል አልነበረም። ግን እነዚህ ዘመናት ሥራ ያልተሠራባቸው፥ ትንቢት ያልተፈጸመባቸው ዘመናት አልነበሩም። እግዚአብሔር የሚሠራ ብቻ ሳይሆን በጊዜ ውስጥ የሚሠራ አምላክ ነው። መልካም ንባብ። ዘላለም መንግሥቱ / ዕዝራ ስነ ጽሑፍ፥ መልአኩም እንዲህ አላት፦ ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም። ሉቃ. ፩፥ ፴-
Less